ከሸይኽ ኡበይድ አልጃቢሪይ
ምክሮች
ምክሮች
ጥያቄ፦
ትዳር ሳትይዝ በመዘግየቷ ሀዘን ውስጥ ተዘፍቃ ላለችዋ እንስት ምን ይመክራሉ ?
ምላሽ፦
ማንኛውም ሰው ወንድም ይሁን ሴት፤ ከሀራም ለመጠበቅ፣ ጉድለቱን ለመጠገንና፣ አላህ የፃፈለትን ልጅ ለማግኘት ሲል፤
ገና በጊዜ ቢያገባ ደስ ይለዋል ይፈልጋልም ።
★ ነገር ግን የብዙሃኑ ሰው ትዳር ይዘገያል፤
በተለይ ደግሞ የእንስቶች ይበልጥ ይዘገያል ።
የእንስቶችን ጉዳይ በተመለከተ፤
አላህ ካዘነለት በስተቀር በሁሉም ስፍራዎች ቤቶች ትዳር በሌላቸው ሴቶች ተሞልተዋል። ከላጤ ሴቶች ነፃ የሆነ ቤት የለም።
ለእነዚህ እንስቶች የምመክረው
1ኛ: ሰብር ( ትዕግስት)
★ መልዕክተኛው ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ለአጎታቸው ልጅ ለዐብደላህ ኢብኑ ዐባስ ረዲየላሁ ዐንሁማ
ረዘም ባለው ሀዲሳቸው እንዳሉት:
ረዘም ባለው ሀዲሳቸው እንዳሉት:
እወቅ (ግንዛቤ ይኑርህ)
ድል ከትዕግስት ጋር ነው!
(ስኬት የሚገኘው በትዕግስት ነው)
ድል ከትዕግስት ጋር ነው!
(ስኬት የሚገኘው በትዕግስት ነው)
ከጭንቀት ግልግልም ከችግር ጋር ነው። (ጭንቀትን ለመገላገል ችግርን መቋቋም ግድ ይላል። )
ከችግር ጋርም ገር ነገር አለ።
ይህንን የነቢዩን صلى الله عليه وسلم
ምክር አትርሺ።
ምክር አትርሺ።
( የምትፈልጊው ምቾት መምጫው ቀርቦ ይሆናልና፤ ያለሽበት ችግር ትካዜ ውስጥ አይዝፈቅሽ )
2ኛ: ዚክር፣ ዱዓእ፣ ቁርኣን መቅራት
yአላህን በማውሳት በዚክር፣
yእሱን በመለመን በዱዓእ፣
yቁርኣንን በመቅራት፣
yበተስቢህ (ሱብሃን አላህ በማለት)
yበተህሊል (ላኢላሃ ኢለላህ
በማለት)
በማለት)
ራስሽን ወጥሪ (ቢዚ አድርጊ)።
በተለይ ምርጥ ወይም ብልጫ ባላቸው ወቅቶች :
የሌሊቱ ሁለት ሶስተኛው ካለፈ
በኋላ
በኋላ
የጁምዓ የመጨረሻዋ ሰዓት ላይ
ዝናብ እየወረደ (እየዘነበ) ባለበት ወቅት፤
ሙስሊሟ፤ ለዲኗም ለዱንያዋም የሚደግፋትን የትዳር ጓደኛ ከአላህ ትለምን።
ዋናው ነገር ባል ማግኘቱ ብቻ አይደለም።
ይህ ባል የሚጠቅማትና የምትደሰትበት ሰው መሆኑ ነው)
አንዳንድ ባሎች ፀጋ (ምቾትና ድሎት) አይደሉም። እንዲያውም ቅጣት፣ መከራና ስቃይ ናቸው።
ስንትና ስንት ሴቶች ናቸው በእንዲህ ዓይነቱ ትዳር ሰበብ በስቃይ ተንገላተው የተፈተኑ።
ከምሬት የተነሳም በወንጀሎች ላይ የወደቁም ቀላል አይደሉም።
3 ኛ : አላህ ከዚህ የላጤነት ችግር እንደሚያወጣት እርግጠኛ መሆን ይገባታል።
~> አላህ እሱን ፈሪ ለሆኑት በሙሉ ቃል የገባዉን (በማሰብ ከችግሯ እንደሚያላቅቃት) እርግጠኛ መሆን አለባት። ይህም ጉዳይ ወንዱንም ሴቷንም የሚያጠቃልል ነው።
قال الله تعالى:
وَمَن يَتَّقِ اللَّهَ يَجْعَل لَّهُ مَخْرَجًا وَيَرْزُقْهُ مِنْ حَيْثُ لَا يَحْتَسِبُ وَمَن يَتَوَكَّلْ عَلَى اللَّهِ فَهُوَ حَسْبُهُ [الطلاق ٢]
“አላህንም የሚፈራ ሰው ለእርሱ መውጫውን ያደርግለታል። ከማያስበውም በኩል ሲሳይን ያደርግለታል” (አል-ጠላቅ 2)
4 ኛ: ወደ ሀዘን አትዘፈቅ
እኔ እንደሚታየኝ ሀዘን ሙስሊሟን ተስፋም ያስቆርጣታል። ተስፋ መቁረጥ ደግሞ ሀራም ነው፤ ጭራሽ ወደ መጥፎ አካባቢዎች ይወስዳትም ይሆናል።
ወደ መጥፎ እርምጃም ይከታት ይሆናል፤
P አላህን ትፍራ
Pትታገስም
ከአላህ ጋርም ትተሳሰብ (በደረሰባት እንግልት ከአላህ መልካምንዳን ትከጅል)
እሱ ያለችበትን ህይወት ወደ መልካሙ የሚቀይርላት ጥራትና ልቅና የተገባው አምላክ ነውና።
5 ኛ: አንዳንድ እንስቶቻችን የሚፈፅሙት ስህተት ኣለ¹
እሱም የሚያጫትን ሰው በራስዋ መንገድ ለራስዋ ማፈላለጓ ነው።
ታፈላልጋለች ከዚያም ወደ ቤተሰቦቿ ታመጣዋለች።
ሁሉም ሰው የየራሱ አስተያየት አለውና እነርሱ ባልተቀበሏት ግዜ ትቆጫለች፣ ቅስሟ ይሰበራል፣ ሀዘንም ላይ ትወድቃለች።
ሙስሊም እንስቶች ሆይ! ይህ አካሄድ ስህተት ነው፤
በቤትሽ እርጊ አላህ የለገሰሽን ዲን ኢስላምን ተላብሰሽ በሃይማኖተኝነትሽ ፅኚ።
ቀድሞ የመከርኩሽንም ደግሜ እመክርሻለሁ
ራስሽን ለውርደት አትዳርጊ
ከውርደትም አንዱ ወንድ ልጅ በውጭ አፈላልገሽ ወደ ቤተሰቦችሽ ማምጣትሽ ነው።
ይህ ደግሞ በባህላችንም ሆነ በሸሪዓችን ጉድለት ነው።
==============
¹ ( ኢስላም የጥፋት በሮችን ከጅምሩ ይዘጋል፤ የሁለትዮሽ ግንኙነትና መለማመድ የሚያስከትሏቸው መዘዞች ከባድ ናቸው። ሸይጣንም ሶስተኛ ነውና አጉል በራስዎ አይተማመኑ።
ይጠንቀቁ –ተርጓሚው―)
ይጠንቀቁ –ተርጓሚው―)
ABU FEWZAN
No comments:
Post a Comment