Tuesday, 21 February 2017

አብረው ከጠቡት ሰው ጋር የስህተት የተፈጸመ ጋብቻ

አብረው ከጠቡት ሰው ጋር የስህተት የተፈጸመ ጋብቻ

የጥቢ ዝምድና መኖሩ በምን ይወሰናል የሚለውን መልስ ማግኘት አጀንዳውን ለመዳሰስ መሰረት ነው።
ሁለት ታማኝ ወንዶች ወይም አንድ ወንድና ሁለት ሴቶች የመሰከሩበት የምስክር ማስረጃ ካለ የጥቢ ዝምድና ይጸድቃል። ይህ ከውዝግብ የራቀና ሁሉንም ኡለማዎች የሚያስማማ የጋራ አቋም ነው። የሀንበሊ መዝሀብ አቋም ከተከታዩ ሀዲሳዊ መረጃ በመነሳት፤ አንዲት በዲኗ የታመነች ሴት እኔ እገሌን፣ እገሌን አጥብቻለው ብላ ማረጋገጫ ከሰጠች የጥቢ ዝምድና መኖሩ ይረጋገጣል ብለዋል (አልሙግኒ 9/222) ሌሎቹ ዘንድ ግን ሀዲሱ አሻሚ ሁኔታዎች ሲከሰቱ ጥንቃቄ ማድረግን የሚያመለክት ብቻ ነው።

ከኡቅበት ቢን ሀሪስ በተዘገበ ሀዲስ ኡቅባህ እንዲህ ይላል። «አንዲት ሴት አገባው። አንዲት ጥቁር ሴቲዮ መጣችና አንተንም እሷንም አጥብቻችኋለው አለችኝ። ነብዩ ዘንድ መጣውና የእገሌን ልጅ እገሊትን አግብቼ ነበር። አንዲት ጥቁር ሴትዮ መጥታ ውሸቷን ሁሌታችሁንም አጥብቻችኋለው አለችን ስላቸው ትተውኝ ዞር አሉ። አሁንም ከፊትለፊታቸው መጥቼ ዋሽታ እኮ ነው አልኳቸው። እሳቸውም “ባለቤትህን ተዋት፤ ሁለታችሁንም አጥብቻለው እያለች እንዴት ይሆናል” በማለት መለሰች» በሌላ ዘገባም የአላህ መልዕክተኛ “እየተወራ እንዴት ይሆናል?” አሉት»  ቡኻሪ በቁጥር 2517 ዘግበውታል

ኢብኑ ሀጀር ሀዲሱን ሲያብራሩ እንዲህ ብለዋል፤ «“እየተወራ እንዴት ይሆናል?” የሚለው ንግግራቸው የሚጠቁመን ባለቤቱን እንዲለያት ያዘዙት ንግግርሯ ትክክል ቢሆን ሀራም እንዳይፈጸም መሆኑን ነው። ይህ ደግሞ ጥንቃቄን መሰረት ካደረገው የብዙሀኑ ኡለማዎች አቋም ጋር አብሮ ይሄዳል። ምስክርነቷን በመቀበል ነው ያሉም አሉ» (ፈትሁል ባሪ 4/374)

በጥቅሉ ይህ ሀዲስ በህጻንነት እንጅ በትልቅነት የተፈጸመ መጥባት ዝምድናን እንደማይፈጥር ከሚያሳዩ መረጃዎች መክካከል ይጠቀሳል። በተጨማሪም በዚህ ጉዳይ ላይ ቸልተኝነት እንደማይገባ ያስገነዝባል።

የሀነፊ መዝሀብ ምሁራን አንድ ወንድና ሁለት ሴቶች የመሰከሩበት ምስክርነት ካልሆነ አይቀበሉም (በዳኢዑ-ሰናኢዕ 4/14) ፤ ማሊኪያዎችም አንዲት ሴት እና አንድ ወንድ መመስከር አለባቸው ብለዋል (ቢዳየቱል ሙጅተሂድ 2/29) ፤ የሻፊዒ ኡለማዕ አራት ሴቶች መመስከር አለባቸው ብለዋል (ሙግኒል ሙህታጅ 3/224) ፤ ሁሉም ለያዙት አቋም መነሻዎች አሏቸው።

ኢብኑ በጧል ይህንን ሀዲስ ሲያብራሩ፤ «ከኢብኑ አባስ፣ ከጧውስ፣ ከዙህሪ፣ ከአውዛዓኢይና ከአህመድ እንዲሁም ከኢስሀቅ እንደተዘገበው፤ ታማኝ የሆነች አንድ ሴት ከመሠከረች በቂ መሆኑን ነው ቢሉም እንደትምል የደረጋል ብለዋል። ይህንን ሀዲስም መረጃ ያደርጋሉ። ከአውዛዒይ እንደተዘገበው ደግሞ ከመጋባታቸው በፊት ከመሰከረች ተቀባይነት አለው ከተጋቡ በኋላ ግን ተቀባይነት የለውም ብለዋል» ከአንድ በላይ ምስክርነትን መስፈርት ያደረጉ አቋሞችን ከዘረዘሩ በኋላ « ከመጀመሪያው አቋም ውጭ ያለውን ያንጸባረቁት ኡለማዎች በዚህ ሀዲስ  “እየተወራ እንዴት ይሆናል?” ያሉትን ጥንቃቄን ከማስቀደም ብቻ እንጂ መለያየታቸው ዋጂብ ሆኖ አለመሆኑን ይጠቅሳሉ። አሊይና ኢብኑ አባስን ተመሳሳይ ጥያቄ ቀርቦላቸው፤ ለጥንቃቄ ቢተዋት መልካም ነው። ነገር ግን እርሱ ላይ እርም ማድረግ ለማንም አይቻለውም። ኡመር ኢብኑል ኸጧብም የአንድን ሴት ብቻ ምስክርንት እንዳላጸደቁ ተነግሯል» ሸርህ ሶሂሁል ቡኻሪ ቅጽ 7 ገጽ 202

የአላህ መልዕክተኛ ጥንቃቄን ማስቀደማቸውን የሚያስረዳ ሌላ ዘገባ አለ። አብዱላህ ኢብኑ መሊካ ከዑቅባ ሰምቻለሁ ይበልጥ የማስታውሰው ግን ጓደኛዪ ከሱ ሰምተው የነገሩኝን ነው ካሉ በኋላ፤ “ኡሙ ያህያ ቢንት አቢ ኢሐብን አገባሁ እና አንዲት ጥቁር ሴት መጥታ አጥብቻችኋለው አለችን። ለመልእክተኛው ስነግራቸው ዝም አሉኝ ደገምኩላቸው ዝም አሉኝ አሁንም ደገምኩላቸውና “ውሸቷን እኮ ነው” ስላቸው፤ “ያለችውን ብላለች፤ አንተ ውሸቷን ስለመሆኑ ምን አሳወቀህ?” ልጅቷን ተዋት አሉኝ» ጦበራኒ ዘግበውታል አልባኒም ሰሂህ ብለውታል (አል ኢርዋዕ 7/225)

በአንድ ባልና ሚስት መካከል መስፈርቶች ተሟልተው በተገኙበት መልኩ የተከሰተ የጥቢ ተዛምዶ መኖሩ ከተረጋገጠ መለያየታቸው ግድ ይሆናል!!

No comments:

Post a Comment