Tuesday, 21 February 2017

ለልጆችህ በራስ የመተማመን ስነ-ልቦና ለመገንባት

ለልጆችህ በራስ የመተማመን  ስነ-ልቦና ለመገንባት
@ ልጅህን በሠዎች ፊት አሞግሠው ፡፡
@ ልጅህ ጥሩ ነገር ሲሰራልህ ፣ ያዘዝከውን ሲፈጽም አመስግናለሁ በለው ፡፡
@ አንድ ነገር አንዲፈጸም ስትፈልግ ቀጥተኛ ትዕዛዝ አታድርግበት ከተመቸህ ይህን እቃ ታቀብለኝ እቃዎችህን በስርዓት ብታስቀምጣቸው ጥሩ ነው ይህን የመሠሉ አገላለጽ ተጠቀም፡፡
@ ልጅህ ልጅነቱን እንዲያጣጥም እድል ስጠው ልጅነቱን እንዲኖር ፍቀድለት፡፡
@ በራሱ ምርጫውን እንዲወስንና አቋም የመያዝ ክህሎቱን እንዲያዳብር ድጋፍ አድርግለት ፡፡
@ ትላልቅ ጥሪዎች ሲኖሩህ ቁም ነገር ያላቸው ከፍተኛ ቦታዎች ስትሄድ በቻልከው አቅም አብሮህ እንዲሆን አድርገው ከሁሉም በላይ ልጅህን ይዘህ ልትሄድ የሚገባው ትልቅና ቁም ነገር ያለው ቦታ መስጅድ ነው።
@ ሐሳብህን አካፍለው ፤ የርሱንም ሐሳብ ጠይቀው ሀሳቡ ከዲን የወጣ እስካልሆነ ድረስ ተቀበለው፡፡
@ በቤት ውስጥ ዐቅም በፈቀደ መጠን የራሱ ክፍል ፣የራሱ ቦታ እንዲኖረው አድርግ ፡፡
@ ጥሩ ጓደኞች እንዲያፈራ ድጋፍ አድረግለት በጓደኞቹ ፊት አትውቀሰው ክብር ስጠው፡፡
@ አላህ ብዙ ችሎታዎችን እንደለገሰው ንገረው ተፈላጊ እና ቦታ የሚሠጠው እንደሆነ እንዲሠማው አደርገው ፡፡
@ ሶላትን አስተምረው አብሮህ እንዲሠግድ አድረግ፡፡
@ በዋነኝነት አላህን እንዲወድ አድርገው ኢማን በልቡ ውስጥ ለማስገባት ጥረት አድርግ ፡፡
@ በአላህ ላይ መመካትን አስተምረው በራስ የመተማመን ስሜቱ በአላህ ላይ ከሚኖረው መደገፍ የመነጨ መሆን እንደሚገባው አስረዳው።
@ ሐሳቡን እንዴት መግለጽ እንደሚችል አስተምረው ሐሳቡን ያለፍርሃት መግለጽ እንዲችል አደፋፍረው ስርዓትን አስተምረው
@ በሠዎች ፊት አትናገር አትበለው ሀሳቡን በማቋረጥ አታሸማቀው።
@ ራሱን ማክበርና ሰዎችን ማክበር እንዴት እንደሚችል አስተምረው ፡፡
@ ጥያቄዎቹን መልስለት፣ ልጅነው ብለህ ቸል አትበለው ፡፡
@ የገባህበትን ቃል አክብር ቃልህን ማክበር የማትችልበት ሁኔታ ከተፈጠረ ቀደም ብልህ አስረዳው ይቅርታም ጠይቀው፡፡
@ ቢያንስ ብቻውን ቢሆን ለራሱ ምግብ ማቅረብ የሚችልበትን ያህል ማብሰል አስተምረው ፡፡
@ ዘወትር ዱዓ ማድረግ እንደሚኖርበት አስተምረው። ሲጨንቀው ወደ አላህ መሸሽ እንዳለበት አስረዳው፡
@ ከሌሎች ልጆችና ከወንድሞቹ/ ከአህቶች ጋር በጋራ መስራትን አስለምደው በቡድን ውስጥ እንዴት ኃላፊነቱን እንደሚወጣ አሳየው፡፡
@ የተለያዩ ምክንያቶች በመደርደር ከሠዎች አታርቀው። ሰዎችን መቅረብ የሚወድ አድርገው ፡፡
@ ጥያቄ እንዲጠይቅ አበረታታው የሚሠነዝራቸውን ጥያቄዎችን «ምን አይነት ጥያቄ ነው» የሚል መልስ በመስጠት አታሸማቀው ከተሳሳተ ስህተቱን አስረዳው ፡፡
@ እርሱን በተመለከተ በምትወስዳቸው ውሳኔዎች ላይ አማክረው፤ ሐሳቦችንና ፍላጎቶቹን አዳምጥ። እርሱ ምን ያውቃል ልጅ ነው ብልህ ፍላጎትህን ብቻ ልትጭንበት አትሞከር።
@ ስለራስህ አጫውተው። በአባቱና በእናቱ ደስተኛ ልጅ እንዲሆን አደርግ።
@ እሺ ማለት ብቻ ሳይሆን የማይስማማውና የማይወደው ነገር ሲኖር እንዴት  እምቢ አይሆንም እንደሚል አስተምረው ፡፡
@ ሲወድቅ ራሱን ችሎ እንዴት መነሳት እንዳለበት አስተምረው፡፡
@ የራሱን ክፍል፣ የራሱን ልብሶች፣ እንዲሁም የራሱን የትምህርት መገልገያዎች ራሱ እንዲያስተካክልና በስርዓት እንዲይዝ አስተምረው ፡፡
@ ስለ ዓላማው ፣ ስለ ህልሙ፣ ስለምኞቱ አዋራው። ሐሳብህን አካፍለው።
@ ኃላፊነቶችን እንዲወስድ አድርግ፡፡
@ ስራዎችን ሲያጠናቀቅ አወድሰው። የማበረታቻ ሽልማቶች ስጠው፡፡
@ ጥፋት ስትፈጽምበት ይቅርታ ጠይቀው፡፡
@ ልዩና አስደሳች ስጦታዎችን ባልጠበቀው ሠዓትና ቦታ ስጠው።
@ ከቁርዓን ጋር ያለው ግንኙነት የጠበቀ እንዲሆን አድርግ ፡፡
@ ስለሶሀቦች የህይወት ታሪክ መፅሀፎችን አንብብለት ፤ ምን ያህል መንፈሰ ጠንካራ መልካም ሰዎች እንደነበሩ አስተምረው፡፡
@ መፅሀፍቶችን እንዲያነብ አበረታታው። በንባብ በሚያገኘውን ዕውቀት በራስ የመተማመን ስነ ልቦናውን እንዲዳብርለት አድርግ ።

@ ዘወትር ዱዓ አድርግለት። አላህን መልካሙን መንገድ እንዲያመላክተው ከክፋት ሁሉ እንዲጠብቀው በወላጅ ልብ ተማፀንለት። ሁሉም መሆን የሚችለው በአላህ ሀይልና ፍቃድ ብቻ ነው። 

No comments:

Post a Comment