ትምህርት ቁጥር 8
#ሂጃብ_የማይለብሱ_እህቶች_የሚያቀርቡት_ምክንያት
ሌላው ሂጃብ አንለብስም ልባችን ንጹህ ነው ብለው ለሚከራከሩ እህቶች :-
አንደኛ ልብ ውስጥ ያለ ኢማን ግዴታ አካል ሊተገብረው ይገባል፡፡ምክንያቱም ኢማን ማለት፡-በልብ የሚታመን በምላስ ሚነገር በአካል ሚተገበር ነው:: ሌላው ደግሞ ያለምንም ሙግትና ክርክር አላህ (ሱብሃነሁ ወተአላ) በሂጃብና በጨዋነት ያዘዛቸው የንጽህና ተምሳሌት ሰሃቦችን ነው:: እንዲህ ብሏል:-
وَإِذَا سَأَلْتُمُوهُنَّ مَتَاعًا فَاسْأَلُوهُنَّ مِن وَرَاءِ حِجَابٍ ۚ ذَٰلِكُمْ أَطْهَرُ لِقُلُوبِكُمْ وَقُلُوبِهِنَّ [٣٣:٥٣]
|ዕቃንም (ለመዋስ) በጠየቃችኋቸው ጊዜ ከመጋረጃ ኋላ ኾናችሁ ጠይቋቸው፡፡ ይህ ለልቦቻችሁ፤ ለልቦቻቸውም የበለጠ ንጽሕና ነው፡፡´ (ምእራፍ አል አህዛብ አንቀጽ 53)
ታዲያ እኛ ከእነርሱ የተሻልን ሆነን ነው ይህንን የምንለው? መልሱን ለአስተንታኞች:: በእርግጥ ስለ ኒቃብ ፊት ስለመሸፈን የሚናገሩ መረጃዎችን በጭሩም ቢሆን ለመዳሰስ ብንሞክር የሚዘለቅ አደለም:: ለማንኛውም ግን ሴት ልጅ ፊቷን መሸፈነ ግዴታ እንደሆነ ተከታዩ አንቀጽም በማያሻማ መልኩ አስቀምጦታል:: አላህ (ሱብሃነሁ ወተአላ) እንዲህ ይላል:-
يَا أَيُّهَا النَّبِيُّ قُل لِّأَزْوَاجِكَ وَبَنَاتِكَ وَنِسَاءِ الْمُؤْمِنِينَ يُدْنِينَ عَلَيْهِنَّ مِن جَلَابِيبِهِنَّ ۚ ذَٰلِكَ أَدْنَىٰ أَن يُعْرَفْنَ فَلَا يُؤْذَيْنَ ۗ وَكَانَ اللَّهُ غَفُورًا رَّحِيمًا [٣٣:٥٩]
|አንተ ነብይ ሆይ ለሚስቶችህ ለሴት ለጆችህም ለምእመናንም ሚስቶችም ከመከናነቢያቸው በላያቸው ላይ እንዲለቁ ንገራቸው ፡፡ይህ እንዲታወቁና (በባለጌዎች) እንዳይደፈሩ ለመሆን በጣም የቀረበ ነው አላህም መሃሪ አዛኝ ነው´ (ምእራፍ አል አህዛብ አንቀጽ 59) ሸይኽ አብድራህማን ቢን ናስር አስሳዕዲ አላህ ይዘንላቸውና ይህን አንቀጽ አስመልክተው እንዲህ ብለዋል ፡- ማለትም “ከልብስ በላይ የሚሆን እንደ መቅለሚያ ጉፍታ ኩታና የመሳሰሉት ሲሆን በእርሱ ፊቶቻቸውንና ደረታቸውን ይሸፍኑ ማለት ነው”::
በእውነቱ የውበት ዋናው መገለጫ ፊት ነው::አንድ ሰው ስለሚወዳት አሊያም ስለሚመኛት ሴት ሲያስብ ከሁሉ በፊት ፊቷን ነው ሚቀርጸው:: ለማየትም ሚቌምጠው ዳሌ ፣ሽንጥ፣ ወገብ እግር ሌላም ሌላም ከፊት በኃላ የሚመጡ ነገሮች ናቸው:: ታዲያ ይህ የውበት መገለጫ ፣ሳቢ መግነጢስ ከሆነ እንዴት መሸፈን የለባትም ይባላል??? መልሱ ለማንም ግልጽ ነው አላህ ሁላችንንም በውስጣዊም በውጫዊም ሂጃብ ያስጊጠን:: አንቺ ውዲቷ እህቴ ኒቃብሽን በመልበስ ደረጃሽን የበለጠ ከፍ ልታደርጊው ይገባል:: ኒቃብ መልበስ ከነገር አለሙ የሚያሰናብት አድርገው ለሚመለከቱ እንዲሁም ለሚሰብኩ ለውጪም ይሁን ለውስጥ ጠላቶችሽ ኒቃብሽን ለብሰሽ ለራስሽም ይሁን ለሌሎች መልካም ነገርን በማበርከት ላይ ፍጹም እንደማያቅብሽ በተግባር አሳያቸው አዎ! ኒቃቤ ውበቴን እንጂ አይምሮዩን አልሸፈነውም በያቸው::
ሌላው ሂጃብ አንለብስም ልባችን ንጹህ ነው ብለው ለሚከራከሩ እህቶች :-
አንደኛ ልብ ውስጥ ያለ ኢማን ግዴታ አካል ሊተገብረው ይገባል፡፡ምክንያቱም ኢማን ማለት፡-በልብ የሚታመን በምላስ ሚነገር በአካል ሚተገበር ነው:: ሌላው ደግሞ ያለምንም ሙግትና ክርክር አላህ (ሱብሃነሁ ወተአላ) በሂጃብና በጨዋነት ያዘዛቸው የንጽህና ተምሳሌት ሰሃቦችን ነው:: እንዲህ ብሏል:-
وَإِذَا سَأَلْتُمُوهُنَّ مَتَاعًا فَاسْأَلُوهُنَّ مِن وَرَاءِ حِجَابٍ ۚ ذَٰلِكُمْ أَطْهَرُ لِقُلُوبِكُمْ وَقُلُوبِهِنَّ [٣٣:٥٣]
|ዕቃንም (ለመዋስ) በጠየቃችኋቸው ጊዜ ከመጋረጃ ኋላ ኾናችሁ ጠይቋቸው፡፡ ይህ ለልቦቻችሁ፤ ለልቦቻቸውም የበለጠ ንጽሕና ነው፡፡´ (ምእራፍ አል አህዛብ አንቀጽ 53)
ታዲያ እኛ ከእነርሱ የተሻልን ሆነን ነው ይህንን የምንለው? መልሱን ለአስተንታኞች:: በእርግጥ ስለ ኒቃብ ፊት ስለመሸፈን የሚናገሩ መረጃዎችን በጭሩም ቢሆን ለመዳሰስ ብንሞክር የሚዘለቅ አደለም:: ለማንኛውም ግን ሴት ልጅ ፊቷን መሸፈነ ግዴታ እንደሆነ ተከታዩ አንቀጽም በማያሻማ መልኩ አስቀምጦታል:: አላህ (ሱብሃነሁ ወተአላ) እንዲህ ይላል:-
يَا أَيُّهَا النَّبِيُّ قُل لِّأَزْوَاجِكَ وَبَنَاتِكَ وَنِسَاءِ الْمُؤْمِنِينَ يُدْنِينَ عَلَيْهِنَّ مِن جَلَابِيبِهِنَّ ۚ ذَٰلِكَ أَدْنَىٰ أَن يُعْرَفْنَ فَلَا يُؤْذَيْنَ ۗ وَكَانَ اللَّهُ غَفُورًا رَّحِيمًا [٣٣:٥٩]
|አንተ ነብይ ሆይ ለሚስቶችህ ለሴት ለጆችህም ለምእመናንም ሚስቶችም ከመከናነቢያቸው በላያቸው ላይ እንዲለቁ ንገራቸው ፡፡ይህ እንዲታወቁና (በባለጌዎች) እንዳይደፈሩ ለመሆን በጣም የቀረበ ነው አላህም መሃሪ አዛኝ ነው´ (ምእራፍ አል አህዛብ አንቀጽ 59) ሸይኽ አብድራህማን ቢን ናስር አስሳዕዲ አላህ ይዘንላቸውና ይህን አንቀጽ አስመልክተው እንዲህ ብለዋል ፡- ማለትም “ከልብስ በላይ የሚሆን እንደ መቅለሚያ ጉፍታ ኩታና የመሳሰሉት ሲሆን በእርሱ ፊቶቻቸውንና ደረታቸውን ይሸፍኑ ማለት ነው”::
በእውነቱ የውበት ዋናው መገለጫ ፊት ነው::አንድ ሰው ስለሚወዳት አሊያም ስለሚመኛት ሴት ሲያስብ ከሁሉ በፊት ፊቷን ነው ሚቀርጸው:: ለማየትም ሚቌምጠው ዳሌ ፣ሽንጥ፣ ወገብ እግር ሌላም ሌላም ከፊት በኃላ የሚመጡ ነገሮች ናቸው:: ታዲያ ይህ የውበት መገለጫ ፣ሳቢ መግነጢስ ከሆነ እንዴት መሸፈን የለባትም ይባላል??? መልሱ ለማንም ግልጽ ነው አላህ ሁላችንንም በውስጣዊም በውጫዊም ሂጃብ ያስጊጠን:: አንቺ ውዲቷ እህቴ ኒቃብሽን በመልበስ ደረጃሽን የበለጠ ከፍ ልታደርጊው ይገባል:: ኒቃብ መልበስ ከነገር አለሙ የሚያሰናብት አድርገው ለሚመለከቱ እንዲሁም ለሚሰብኩ ለውጪም ይሁን ለውስጥ ጠላቶችሽ ኒቃብሽን ለብሰሽ ለራስሽም ይሁን ለሌሎች መልካም ነገርን በማበርከት ላይ ፍጹም እንደማያቅብሽ በተግባር አሳያቸው አዎ! ኒቃቤ ውበቴን እንጂ አይምሮዩን አልሸፈነውም በያቸው::
No comments:
Post a Comment